የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
አማርኛ ጽሑፎች (1991-2026)
ውጣ
ግባ
የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • ዛሬ

ረቡዕ፣ ሚያዝያ 29

የማመዛዘን ችሎታ ምንጊዜም ይጠብቅሃል፤ ጥልቅ ግንዛቤም ይጋርድሃል።—ምሳሌ 2:11

በየዕለቱ ውሳኔዎችን ማድረግ ያስፈልገናል። አንዳንዶቹን ውሳኔዎች ማድረግ ቀላል ነው፤ ለምሳሌ ‘ቁርስ ምን ልብላ’ ወይም ‘ስንት ሰዓት ልተኛ’ የሚለውን መወሰን ቀላል ነው። አንዳንዶቹን ውሳኔዎች ማድረግ ግን ከባድ ሊሆን ይችላል። እነዚህ ውሳኔዎች በጤንነታችን፣ በደስታችን፣ በወዳጅ ዘመዶቻችን ወይም በአምልኳችን ላይ ተጽዕኖ ሊያሳድሩ ይችላሉ። እኛንም ሆነ ቤተሰቦቻችንን የሚጠቅሙ ውሳኔዎችን ማድረግ እንፈልጋለን። ከሁሉ በላይ ደግሞ ውሳኔዎቻችን ይሖዋን የሚያስደስቱ እንዲሆኑ እንፈልጋለን። (ሮም 12:1, 2) ጥሩ ውሳኔ ለማድረግ የሚረዳህ አንዱ ወሳኝ እርምጃ የተሟላ መረጃ ማግኘት ነው። ለምን? ለምሳሌ አንድ ታማሚ ያጋጠመውን ከባድ የጤና ችግር አስመልክቶ ሐኪሙን አማከረ እንበል። ሐኪሙ በመጀመሪያ ታማሚውን ሳይመረምረው ወይም ጥያቄዎችን ሳይጠይቀው ምን ዓይነት ሕክምና እንደሚሰጠው ይወስናል? እንዲህ እንደማያደርግ የታወቀ ነው። አንተም በመጀመሪያ ከጉዳዩ ጋር የተያያዙ መረጃዎችን ለማግኘት ጥረት ካደረግክ ጥሩ ውሳኔ ማድረግ ትችላለህ። w25.01 14 አን. 1-3

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2026

ሐሙስ፣ ሚያዝያ 30

ይሖዋ . . . ኃጢአትህን ይቅር ይላል። አትሞትም።—2 ሳሙ. 12:13

የይሖዋን ምሕረት በተመለከተ ምን እናውቃለን? ይሖዋ ‘ማንም እንዲጠፋ እንደማይፈልግ’ ያሳየው እንዴት ነው? (2 ጴጥ. 3:9) ከባድ ኃጢአት ለፈጸሙ አንዳንድ ሰዎች ያሳየውን ምሕረት እንመልከት። ንጉሥ ዳዊት ምንዝርንና ነፍስ ግድያን ጨምሮ ከባድ ኃጢአቶችን ፈጽሟል። ያም ቢሆን ዳዊት ንስሐ ስለገባ ይሖዋ በምሕረት ይቅር ብሎታል። (2 ሳሙ. 12:1-12) ንጉሥ ምናሴ በአብዛኛው የሕይወቱ ክፍል እጅግ ክፉ ሰው ነበር። ይሁንና በጣም ክፉ የነበረው ይህ ሰውም እንኳ ንስሐ ሲገባ ይሖዋ ምሕረት በማሳየት ይቅር ብሎታል። (2 ዜና 33:9-16) እነዚህ ምሳሌዎች፣ ይሖዋ ምሕረት ለማሳየት የሚያስችል መሠረት እስካገኘ ድረስ ምሕረት እንደሚያሳይ ያስታውሱናል። እንዲህ ያሉት ሰዎች ከባድ ኃጢአት መፈጸማቸውን ተገንዝበው ንስሐ ስለገቡ ይሖዋ ከሞት ያስነሳቸዋል። w24.05 4 አን. 12

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2026

ዓርብ፣ ግንቦት 1

በአምላክ ዘንድ አድልዎ የለም።—ሮም 2:11

ይሖዋ ሕዝቡን ከግብፅ ባርነት ነፃ ካወጣቸው በኋላ በማደሪያው ድንኳን የሚያገለግሉ ካህናትን ሾመ። ሌዋውያን ደግሞ ከቅዱሱ ድንኳን ጋር በተያያዘ ሌሎች ኃላፊነቶች ነበሯቸው። ይሖዋ በማደሪያ ድንኳኑ ውስጥ ለሚያገለግሉ ወይም በአቅራቢያው ለሰፈሩ እስራኤላውያን የተለየ እንክብካቤ ያደርግላቸው ነበር? በፍጹም! ይሖዋ አያዳላም። ሁሉም እስራኤላውያን የይሖዋ ወዳጆች የመሆን እኩል አጋጣሚ ነበራቸው። ለምሳሌ ይሖዋ በማደሪያ ድንኳኑ ላይ ያለውን ተአምራዊ የደመና ዓምድና የእሳት ዓምድ መላው ብሔር ማየት እንዲችል አድርጎ ነበር። (ዘፀ. 40:38) ደመናው መንቀሳቀስ ሲጀምር ከማደሪያ ድንኳኑ በጣም ርቀው የሰፈሩ እስራኤላውያን እንኳ ማየት ይችሉ ነበር፤ እነሱም ዕቃቸውን ሰብስበው፣ ድንኳናቸውን አፍርሰው ከቀረው ብሔር ጋር መጓዝ ይችላሉ። (ዘኁ. 9:15-23) ዛሬም በተመሳሳይ የምንኖረው የትም ይሁን የት የይሖዋን ፍቅራዊ እንክብካቤና ጥበቃ ማግኘት እንችላለን። w24.06 4 አን. 10-12

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2026
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2026 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ