የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
ውጣ
ግባ
የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • ዛሬ

ማክሰኞ፣ ጥር 27

እጆቼን ለውጊያ . . . የሚያሠለጥነው፣ ዓለቴ የሆነው ይሖዋ ይወደስ።—መዝ. 144:1

ትክክል የሆነውን ነገር ለማድረግ ቆራጥ ከሆንንና በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረታዊ ሥርዓቶች ላይ የተመሠረቱ ውሳኔዎችን የምናደርግ ከሆነ በሌሎች ላይ በጎ ተጽዕኖ እናሳድራለን። በእምነትና በትክክለኛ እውቀት እያደግን ስንሄድ በእውነት ውስጥ ሥር እንሰዳለን። ወላዋይ፣ ጽኑ አቋም የሌለን ወይም በሐሰት ትምህርቶችና በዓለም አስተሳሰብ እየተገፋን በቀላሉ ወዲያና ወዲህ የምንዋልል ሰዎች አይደለንም። (ኤፌ. 4:14፤ ያዕ. 1:6-8) መከራ ያጋጠማቸውን ሰዎች መርዳትም እንችላለን። (1 ተሰ. 3:2, 3) ሽማግሌዎች በልማዶቻቸው ልከኛ፣ ጤናማ አስተሳሰብ ያላቸው፣ ሥርዓታማና ምክንያታዊ መሆን ይጠበቅባቸዋል። እነዚህ ወንዶች ‘የታመነውን ቃል በጥብቅ በመከተል’ ሌሎች ጠንካራ አቋም እንዲኖራቸው ይረዳሉ። (ቲቶ 1:9፤ 1 ጢሞ. 3:1-3) ሽማግሌዎች ጥሩ ምሳሌ በመሆንና እረኝነት በማድረግ አስፋፊዎች አዘውትረው በጉባኤ ስብሰባዎች ላይ እንዲገኙ፣ በአገልግሎት እንዲካፈሉ እንዲሁም የግል ጥናት እንዲያደርጉ ይረዳሉ። ሽማግሌዎች፣ ወንድሞችና እህቶች አስጨናቂ ሁኔታ ሲያጋጥማቸው በይሖዋና በዓላማዎቹ ላይ እንዲያተኩሩ ሊረዷቸው ይችላሉ። w24.06 31 አን. 16-18

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2026

ረቡዕ፣ ጥር 28

መንግሥተ ሰማያት ስለቀረበ ንስሐ ግቡ።—ማቴ. 4:17

ኢየሱስ በምድራዊ አገልግሎቱ ወቅት አባቱ ምን ያህል ይቅር ባይ እንደሆነ አስተምሯል። የአባካኙን ልጅ ምሳሌ እንመልከት። ያ ወጣት ለተወሰነ ጊዜ ያህል የኃጢአት ጎዳና ለመከተል መርጦ ነበር። ያም ቢሆን “ወደ ልቦናው ሲመለስ” ወደ ቤቱ ሄደ። በዚህ ጊዜ አባቱ ምን አደረገ? ኢየሱስ እንዲህ ብሏል፦ “[ልጁ] ገና ሩቅ ሳለም አባቱ አየው፤ . . . እየሮጠ ሄዶም አንገቱ ላይ ተጠምጥሞ ሳመው።” ልጁ ከአባቱ አገልጋዮች እንደ አንዱ ተደርጎ ለመቆጠር ፈቃደኛ ነበር። አባቱ ግን “ይህ ልጄ” በማለት ጠርቶታል፤ በድጋሚ የቤተሰቡ አባል አድርጎም ተቀብሎታል። አባቱ “ጠፍቶ ነበር፤ ተገኝቷል” ብሏል። (ሉቃስ 15:11-32) ኢየሱስ ወደ ምድር ከመምጣቱ በፊት ሰማይ ላይ ሳለ አባቱ ስፍር ቁጥር ለሌላቸው ንስሐ የገቡ ኃጢአተኞች እንዲህ ያለ ርኅራኄ ሲያሳይ እንደተመለከተ ምንም ጥያቄ የለውም። ኢየሱስ የተናገረው ልብ የሚነካ ታሪክ አባታችን ይሖዋ እጅግ መሐሪ እንደሆነ ያሳያል። ይህ ምንኛ የሚያጽናና ነው! w24.08 11 አን. 11-12

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2026

ሐሙስ፣ ጥር 29

ጤናማ አስተሳሰብ ይኑራችሁ።—1 ጴጥ. 4:7

ጤናማ አስተሳሰብ ያለው አንድ ክርስቲያን ውሳኔ ሲያደርግ የይሖዋን አስተሳሰብ ለማንጸባረቅ ይጥራል። በሕይወቱ ውስጥ ከይሖዋ ጋር ካለው ዝምድና በላይ ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ ነገር እንደሌለ ይገነዘባል። ስለ ራሱ ሚዛናዊ አመለካከት አለው፤ የማያውቃቸው ነገሮች እንዳሉም ይረዳል። ደግሞም ምንጊዜም የይሖዋ እርዳታ እንደሚያስፈልገው በትሕትና ስለሚገነዘብ አዘውትሮ ይጸልያል። ምንም ዓይነት ተፈጥሯዊ ተሰጥኦ ቢኖረን ምንጊዜም የይሖዋን እርዳታ መጠየቅ አስፈላጊ እንደሆነ እንገነዘባለን። በተለይ ከበድ ያሉ ውሳኔዎችን ከማድረጋችን በፊት ይሖዋ እንዲመራን እንጸልያለን፤ ምክንያቱም ለእኛ የሚበጀውን የሚያውቀው እሱ እንደሆነ እንተማመናለን። ይሖዋ የእሱን ባሕርያት ማንጸባረቅ እንድንችል አድርጎ ስለፈጠረን በጣም አመስጋኞች ነን። (ዘፍ. 1:26) ይሖዋን ፍጹም በሆነ መንገድ መምሰል እንደማንችል የታወቀ ነው።—ኢሳ. 55:9፤ w25.03 11 አን. 13፤ 13 አን. 17-18

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2026
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2026 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ