የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2026)
ውጣ
ግባ
የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
ማስታወቂያ
አዲስ የገባ ቋንቋ፦ Dengese
  • ዛሬ

ዓርብ፣ ሚያዝያ 10

ሕግህን ምንኛ ወደድኩ! ቀኑን ሙሉ አሰላስለዋለሁ።—መዝ. 119:97

መጽሐፍ ቅዱስን ስታነብ ትምህርቱን ተግባራዊ የምታደርግባቸውን መንገዶች ፈልግ። የተወሰነ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ካነበብክ በኋላ ራስህን እንዲህ ብለህ ጠይቅ፦ ‘በአሁኑ ወቅት ወይም በቅርቡ ይህን ትምህርት ተግባራዊ ማድረግ የምችለው እንዴት ነው?’ ለምሳሌ የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብህ 1 ተሰሎንቄ 5:17, 18ን ያካተተ ነው እንበል። ይህን ጥቅስ ካነበብክ በኋላ ስለ ጸሎት ልማድህ ቆም ብለህ ልታስብ ትችላለህ። ምን ያህል አዘውትረህ ትጸልያለህ? ጸሎትህስ ምን ያህል ጥልቀት ያለው ነው? ልታስብበት የምትችለው ሌላው ነገር ደግሞ ‘ስለ የትኞቹ ነገሮች አመስጋኝ መሆን እችላለሁ?’ የሚለው ነው። ምናልባት ሦስት ነገሮችን ጠቅሰህ ይሖዋን ለማመስገን ልትወስን ትችላለህ። ለጥቂት ደቂቃዎች ብቻ እንኳ ትኩረትህን ሰብስበህ ማሰብህ የአምላክን ቃል የምትሰማና የምታደርግ እንድትሆን የሚረዳህ እንዴት እንደሆነ አስተዋልክ? በየዕለቱ ከምታደርገው የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ ጋር በተያያዘ ይህንኑ ብታደርግ ምን ያህል ልትጠቀም እንደምትችል እስቲ አስበው! አዎ፣ የአምላክን ቃል በማድረግ ረገድ እየተሻሻልክ ትሄዳለህ። w24.09 4-5 አን. 9-10

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2026

ቅዳሜ፣ ሚያዝያ 11

ሙሉ ሽልማት እንድታገኙ እንጂ የደከምንባቸውን ነገሮች እንዳታጡ ለራሳችሁ ተጠንቀቁ።—2 ዮሐ. 8

ይሖዋ የፈጠረን ልዩ ችሎታ ሰጥቶ ነው። መቀበል የሚያስደስተን ቢሆንም ስንሰጥ የበለጠ ደስታ እናገኛለን። የእምነት አጋሮቻችንን ስንረዳ ደስ ይለናል። ምስጋናቸውን ሲገልጹልንም እንደሰታለን። ይሁንና ልግስና ያሳየናቸው ሰዎች ቢያመሰግኑንም ባያመሰግኑንም ትክክል የሆነውን ነገር በማድረጋችን መደሰት እንችላለን። ለሌሎች የምትሰጠው ነገር ምንም ይሁን ምን “ይሖዋ ከዚህ እጅግ የሚበልጥ ሊሰጥህ [እንደሚችል]” ፈጽሞ አትርሳ። (2 ዜና 25:9) መቼም ቢሆን ይሖዋ ከሚሰጠን ይበልጥ መስጠት አንችልም! ደግሞም በይሖዋ ከመካስ የበለጠ አስደሳች ነገር የለም። እንግዲያው ለጋስ የሆነውን የሰማዩን አባታችንን መምሰላችንን ለመቀጠል ቁርጥ ውሳኔ እናድርግ። w24.09 31 አን. 20-21

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2026

እሁድ፣ ሚያዝያ 12

ይሖዋ አምላኬ ሆይ፣ በሙሉ ልቤ አወድስሃለሁ፤ ስምህንም ለዘላለም ከፍ ከፍ አደርጋለሁ።—መዝ. 86:12

ይሖዋ መሐሪና ሩኅሩኅ ነው። (መዝ. 103:13፤ ኢሳ. 49:15) ስሜታችንን ይረዳልናል፤ ሥቃያችን ይሰማዋል። (ዘካ. 2:8) ወደ እሱ እንድንቀርብና ወዳጆቹ እንድንሆን ፈቅዶልናል። (መዝ. 25:14፤ ሥራ 17:27) ትሑት ነው፤ “ሰማይንና ምድርን ለማየት ወደ ታች ያጎነብሳል፤ ችግረኛውን ከአፈር ያነሳል።” (መዝ. 113:6, 7) ታዲያ ለታላቁ አምላካችን ክብር ለመስጠት ብንነሳሳ ምን ያስገርማል? ለይሖዋ ክብር የምንሰጠው ሌሎች ስለ እሱ እንዲያውቁ ስለምንፈልግ ነው። ብዙዎች ስለ ይሖዋ እውነቱን አያውቁም። ለምን? ምክንያቱም ሰይጣን ስለ ይሖዋ መርዘኛ ውሸቶችን በመንዛት አእምሯቸውን አሳውሯል። (2 ቆሮ. 4:4) ሰይጣን፣ ይሖዋ በቀለኛ፣ ለሰዎች የማያስብ እንዲሁም በዓለም ላይ ላሉት ችግሮች መንስኤ እንደሆነ ሰዎችን አሳምኗል። እኛ ግን ስለ አምላካችን እውነቱን እናውቃለን! ስለ ይሖዋ እውነቱን በመናገር ለእሱ ክብር የማምጣት አጋጣሚ አግኝተናል።—ኢሳ. 43:10፤ w25.01 3 አን. 6-7

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2026
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2026 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ