የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2026)
ውጣ
ግባ
የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • ዛሬ

እሁድ፣ ሐምሌ 12

የተወደዳችሁ ወንድሞች፣ ራሳችሁ አትበቀሉ፤ ከዚህ ይልቅ “‘በቀል የእኔ ነው፤ እኔ ብድራትን እመልሳለሁ’ ይላል ይሖዋ” ተብሎ ስለተጻፈ ለቁጣው ዕድል ስጡ።—ሮም 12:19

ሐዋርያው ጳውሎስ ለይሖዋ ‘ቁጣ ዕድል እንዲሰጡ’ ክርስቲያኖችን መክሯቸዋል። ለይሖዋ ቁጣ ዕድል የምንሰጠው እሱ በመረጠው ጊዜና በመረጠው መንገድ ችግሩን እንዲያስተካክል በመፍቀድ ነው። ጆን የተባለ ወንድም ኢፍትሐዊ ድርጊት ከተፈጸመበት በኋላ እንዲህ ብሏል፦ “በራሴ መንገድ ችግሩን ለማስተካከል ተፈትኜ ነበር። ሆኖም ሮም 12:19 ይሖዋን እንድጠብቅ ረድቶኛል።” ይሖዋ ችግሩን እስኪያስተካክል መጠበቃችን ይጠቅመናል። እንዲህ ካደረግን፣ በራሳችን መንገድ ችግሩን ለመፍታት መሞከር ከሚያስከትለው ሸክምና ብስጭት እንጠበቃለን። ይሖዋ ሊረዳን ፈቃደኛ ነው። “ጉዳዩን ለእኔ ተዉት። እኔ ራሴ አስተካክለዋለሁ” እንዳለን ሊቆጠር ይችላል። ይሖዋ “እኔ ብድራትን እመልሳለሁ” በማለት በገባው ቃል ከተማመንን እሱ ከሁሉ በተሻለ መንገድ ችግሩን እንደሚያስተካክለው እርግጠኛ በመሆን ጉዳዩን ለእሱ መተው እንችላለን። w24.11 6 አን. 14-15

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2026

ሰኞ፣ ሐምሌ 13

የዕለቱን ምግባችንን ለዕለቱ የሚያስፈልገንን ያህል ስጠን።—ሉቃስ 11:3

ለቁሳዊ ነገሮች ከተገቢው ያለፈ ትኩረት ልንሰጥ አይገባም። ሐዋርያው ጳውሎስ በአይሁድ ሥርዓት መደምደሚያ ላይ ይኖሩ ለነበሩት ክርስቲያኖች በጻፈበት ወቅት ይህን ሐሳብ ጎላ አድርጎ ገልጿል። ጳውሎስ እስራኤላውያን በጥንት ዘመን ያጋጠሟቸውን ነገሮች ጠቅሷል፤ ከእነዚህም መካከል በሲና ተራራ አቅራቢያ ያደረጉት ነገር ይገኝበታል። “[እስራኤላውያን] ጎጂ የሆኑ ነገሮችን እንደተመኙ እኛም እንዳንመኝ” በማለት ለክርስቲያኖች ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል። (1 ቆሮ. 10:6, 7, 11) እስራኤላውያን የምግብ ፍላጎታቸው ይሖዋ በተአምር ያደረገላቸው ዝግጅትም እንኳ ‘ጎጂ ነገር’ እንዲሆንባቸው አድርጓል። (ዘኁ. 11:4-6, 31-34) የወርቅ ጥጃ በሠሩበት ጊዜ ደግሞ በልተዋል፣ ጠጥተዋል እንዲሁም ጨፍረዋል። (ዘፀ. 32:4-6) ጳውሎስ የጥንቶቹ እስራኤላውያን ያጋጠማቸውን ነገር በ70 ዓ.ም. የአይሁድ ሥርዓት መጨረሻ ከመምጣቱ በፊት ለኖሩት ክርስቲያኖች ማስጠንቀቂያ አድርጎ ጠቅሶታል። እኛም የምንኖረው የዚህ ሥርዓት መጨረሻ በተቃረበበት ዘመን ስለሆነ የጳውሎስን ምክር በቁም ነገር ልንመለከተው ይገባል። w24.12 6 አን. 13

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2026

ማክሰኞ፣ ሐምሌ 14

ከወጣትነት [ሚስትህ] ጋር ደስ ይበልህ።—ምሳሌ 5:18

ይሖዋ ‘ደስተኛ አምላክ’ ነው፤ እኛም ደስተኞች እንድንሆን ይፈልጋል። (1 ጢሞ. 1:11) በሕይወታችን ደስተኛ እንድንሆን የሚያስችሉንን ብዙ ስጦታዎች ሰጥቶናል። (ያዕ. 1:17) ከእነዚህ ስጦታዎች አንዱ ትዳር ነው። አንድ ወንድና አንዲት ሴት ሲጋቡ አንዳቸው ሌላውን ለመውደድ፣ ለማክበርና ለመንከባከብ ቃል ይገባሉ። ፍቅራቸውን እያጠናከሩ መኖራቸው እውነተኛ ደስታ ያስገኝላቸዋል። የሚያሳዝነው፣ በዛሬው ጊዜ ያሉ ብዙ ባለትዳሮች በሠርጋቸው ዕለት የገቡትን ቃል ይረሳሉ። በዚህም ምክንያት ደስታ ርቋቸዋል። ይሖዋ፣ ባሎች ሚስቶቻቸውን በምን መንገድ እንዲይዙ ይጠብቅባቸዋል? ይሖዋ፣ ባሎች ሚስቶቻቸውን እንዲያከብሩ አዟቸዋል። ሚስቱን የሚያከብር ባል ደግነትና ፍቅር በሚንጸባረቅበት መንገድ ይይዛታል።—1 ጴጥ. 3:7፤ w25.01 8 አን. 1-2፤ 9 አን. 4-5

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2026
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2026 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ