የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2026)
ውጣ
ግባ
የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • ዛሬ

ሰኞ፣ የካቲት 23

ይሖዋ . . . እናንተን የታገሠው፣ ሁሉ ለንስሐ እንዲበቃ እንጂ ማንም እንዲጠፋ ስለማይፈልግ ነው።—2 ጴጥ. 3:9

ሐዋርያው ጴጥሮስ በሕይወቱ ያየው ነገር ስላለ ለሌሎች ስለ ንስሐና ስለ ይቅርታ ሊያስተምር ችሏል። ከጴንጤቆስጤ በዓል በኋላ ጴጥሮስ አማኝ ላልሆኑ አይሁዳውያን ንግግር ባቀረበበት ወቅት መሲሑን እንደገደሉት ነግሯቸዋል። ሆኖም እንዲህ የሚል ፍቅራዊ ማሳሰቢያ ሰጣቸው፦ “ኃጢአታችሁ እንዲደመሰስ ንስሐ ግቡ፣ ተመለሱም፤ ከይሖዋም ዘንድ የመታደስ ዘመን ይመጣላችኋል።” (ሥራ 3:14, 15, 17, 19) በዚህ መንገድ ጴጥሮስ፣ ንስሐ አንድን ኃጢአተኛ እንዲመለስ ማለትም የተሳሳተ አስተሳሰቡንና ምግባሩን እንዲያስተካክል እንዲሁም አምላክን የሚያስደስት አዲስ ጎዳና እንዲከተል እንደሚያነሳሳው አሳይቷል። በተጨማሪም ጴጥሮስ፣ ይሖዋ ኃጢአታቸውን እንደሚደመስስላቸው ነግሯቸዋል። ከባድ ኃጢአት ብንፈጽምም እንኳ ይሖዋ ይቅር እንደሚለን ማወቅ ምንኛ የሚያጽናና ነው! w24.08 12 አን. 14

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2026

ማክሰኞ፣ የካቲት 24

አኗኗራችሁ ከገንዘብ ፍቅር ነፃ ይሁን።—ዕብ. 13:5

የዚህ ሥርዓት መጨረሻ በቅርቡ እንደሚመጣ ጠንካራ እምነት ካለን ከፍቅረ ነዋይ ለመራቅ እንነሳሳለን። ሰዎች “በይሖዋ የቁጣ ቀን ብራቸውም ሆነ ወርቃቸው ሊያድናቸው” እንደማይችል ስለሚገነዘቡ “ብራቸውን በየጎዳናው ይጥላሉ።” (ሕዝ. 7:19) የምንችለውን ያህል ብዙ ገንዘብ በማከማቸት ላይ ትኩረት ከማድረግ ይልቅ ቀላል ሆኖም ሚዛናዊ ሕይወት ለመምራት የሚረዱንን ውሳኔዎች ማድረግ ይኖርብናል። ለምሳሌ አላስፈላጊ ዕዳ ውስጥ ከመግባት ወይም የእኛን ጊዜና እንክብካቤ የሚፈልጉ ብዙ ቁሳዊ ነገሮችን ከመሰብሰብ እንቆጠባለን። አሁን ላሉን ቁሳዊ ንብረቶችም ከመጠን ያለፈ ፍቅር እንዳይኖረን እንጠነቀቃለን። (ማቴ. 6:19, 24) የዚህን ሥርዓት መጨረሻ በምንጠባበቅበት ወቅት ከቁሳዊ ነገሮችም ሆነ ከሌሎች ነገሮች ጋር በተያያዘ እምነታችን ሊፈተን ይችላል። w24.09 11 አን. 13-14

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2026

ረቡዕ፣ የካቲት 25

የቆመ የሚመስለው እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ።—1 ቆሮ. 10:12

አንዳንድ ድክመቶቻችንን ሙሉ በሙሉ ማሸነፍ እንችል ይሆናል። ይሁንና ሌሎች ዝንባሌዎች በቀጣይነት ሊያታግሉን ይችላሉ። የሐዋርያው ጴጥሮስን ሁኔታ እንደ ምሳሌ እንውሰድ። ኢየሱስን ሦስት ጊዜ የካደው ለሰው ፍርሃት እጅ በመስጠቱ ነው። (ማቴ. 26:69-75) ጴጥሮስ በሳንሄድሪን ሸንጎ ፊት በድፍረት ምሥክርነት በሰጠበት ወቅት ፍርሃቱን ማሸነፍ የቻለ ይመስል ነበር። (ሥራ 5:27-29) ይሁንና ከተወሰኑ ዓመታት በኋላ “ከተገረዙት ወገን የሆኑትን በመፍራት” ለተወሰነ ጊዜ ያህል ከአሕዛብ ክርስቲያኖች ጋር መብላት አቁሞ ነበር። (ገላ. 2:11, 12) ጴጥሮስ ፍርሃቱ አገርሽቶበታል። ምናልባት ቀድሞውንም ይህን ድክመት ሙሉ በሙሉ አላሸነፈው ይሆናል። እኛም ተመሳሳይ ሁኔታ ሊያጋጥመን ይችላል። እያታገለን ያለ ዝንባሌ ካለ ኢየሱስ “ነቅታችሁ ጠብቁ” በማለት የሰጠውን ምክር መከተላችን በፈተናው እንዳንሸነፍ ይረዳናል። (ማቴ. 26:41) ጠንካራ እንደሆንክ በሚሰማህ ጊዜም ጭምር ወደ ፈተና ሊመሩህ ከሚችሉ ሁኔታዎች መራቅህን ቀጥል። እንዲሳካልህ የረዱህን ዘዴዎች በሥራ ላይ ማዋልህን አታቋርጥ።—2 ጴጥ. 3:14፤ w24.07 18 አን. 17-19

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2026
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2026 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ