የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2026)
ውጣ
ግባ
የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • ዛሬ

ዓርብ፣ ሐምሌ 31

በእምነት ጸንታችሁ ቁሙ።—1 ቆሮ. 16:13

የምታከናውነውን ነገር ከሌሎች ጋር ለማወዳደር ትፈተን ይሆናል። ሆኖም እንዲህ ልታደርግ አይገባም። ለምን? ምክንያቱም ይሖዋ ሰዎችን በዚህ መልኩ አያወዳድርም። (ገላ. 6:4) ለምሳሌ ማርያም ለኢየሱስ እጅግ ውድ የሆነና ጥሩ መዓዛ ያለው ዘይት ሰጥታው ነበር። (ዮሐ. 12:3-5) ድሃዋ መበለት ደግሞ በቤተ መቅደሱ መዋጮ ያደረገችው በጣም አነስተኛ ዋጋ ያላቸውን ሁለት ትናንሽ ሳንቲሞች ነው። (ሉቃስ 21:1-4) ሆኖም ኢየሱስ እነዚህን ሴቶች አላወዳደራቸውም። ከዚህ ይልቅ ያተኮረው ሁለቱም ባሳዩት እምነት ላይ ነው። ኢየሱስ የአባቱ ፍጹም ነጸብራቅ ነው። የምታከናውነው ነገር ለአንተ በጣም ትንሽ ቢመስልህም እንኳ ለይሖዋ ባለህ ፍቅርና ታማኝነት ተነሳስተህ እስካደረግከው ድረስ በእሱ ዘንድ ትልቅ ዋጋ አለው። ሁላችንም አልፎ አልፎ ጥርጣሬ ያድርብናል። ይሁንና አስተማማኝና እውነተኛ የሆነው የአምላክ ቃል ጥርጣሬያችንን ለማሸነፍ ይረዳናል። ጥርጣሬህን በእምነት ተካው። ይሖዋ በግለሰብ ደረጃ ትኩረት ይሰጥሃል። የከፈልካቸውን መሥዋዕቶች ያደንቃል፤ ወሮታ እንደሚከፍልህም ቃል ገብቷል። ይሖዋ ሁሉንም ታማኝ አገልጋዮቹን ይወዳቸዋል እንዲሁም ትኩረት ይሰጣቸዋል። w24.10 25 አን. 3፤ 29 አን. 17-18

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2026

ቅዳሜ፣ ነሐሴ 1

ከዓለም መጀመሪያ አንስቶ እስካሁን ድረስ ሆኖ የማያውቅ ዳግመኛም የማይሆን ታላቅ መከራ ይከሰታል።—ማቴ. 24:21

በተቻለ መጠን ብዙ ሰዎች ለማስጠንቀቂያችን ምላሽ በመስጠት ከአሁኑ በንጹሕ አምልኮ አብረውን መካፈል እንዲጀምሩ እንጸልያለን። ይሁንና የምንወዳቸውን ቤተሰቦቻችንን ጨምሮ በአሁኑ ወቅት ይህን ማስጠንቀቂያ ልብ ስለማይሉ ሰዎችስ ምን ማለት ይቻላል? ባለፈው ርዕስ ላይ እንደተመለከትነው፣ ይሖዋ የታላቂቱ ባቢሎንን ጥፋት ሲያዩ አቋማቸውን የሚያስተካክሉ ሰዎችን ለማዳን ሊወስን ይችላል። ሁኔታው እንደዚያ ከሆነ፣ ማስጠንቀቂያውን ማሰማታችንን መቀጠላችን ይበልጥ አንገብጋቢ ነው ማለት ነው። አሁን የምንነግራቸው ነገር ወደፊት የሚያስታውሱት ነገር እንዲኖር ያደርጋል። (ከሕዝቅኤል 33:33 ጋር አወዳድር።) ምናልባትም ከእኛ የሰሙትን ማስጠንቀቂያ አስታውሰው ጊዜው ከማለፉ በፊት በንጹሕ አምልኮ አብረውን ለመካፈል ይነሳሱ ይሆናል። በፊልጵስዩስ የነበረው የእስር ቤት ጠባቂ አመለካከቱን የቀየረው “ከባድ የምድር ነውጥ” ከተከሰተ በኋላ እንደነበረ ሁሉ አሁን ምላሽ የማይሰጡ አንዳንድ ሰዎች ምድርን የሚያናውጥ ክንውን ከሆነው ከታላቂቱ ባቢሎን ጥፋት በኋላ አመለካከታቸውን ይቀይሩ ይሆናል።—ሥራ 16:25-34፤ w24.05 17 አን. 9-10

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2026

እሁድ፣ ነሐሴ 2

ክርስቶስ የሕግ ፍጻሜ ነው።—ሮም 10:4

ሐዋርያው ጳውሎስ ለዕብራውያን ክርስቲያኖች ከጻፈላቸው ሐሳብ ጠቃሚ ትምህርት እናገኛለን። አንዳንዶቹ መንፈሳዊ እድገት ማድረጋቸውን አቁመው ነበር። እንዲያውም “ጠንካራ [መንፈሳዊ] ምግብ ከመመገብ ይልቅ እንደገና ወተት መፈለግ” ጀምረው ነበር። (ዕብ. 5:12) በጉባኤው አማካኝነት ደረጃ በደረጃ እየተገለጠ ካለው እውነት ጋር እኩል መሄድ ተስኗቸዋል። (ምሳሌ 4:18) ለምሳሌ ከ30 ዓመት ገደማ በፊት ሕጉ በክርስቶስ መሥዋዕት አማካኝነት የተሻረ ቢሆንም በርካታ አይሁዳውያን ክርስቲያኖች አሁንም የሙሴን ሕግ ይከተሉ ነበር። (ቲቶ 1:10) ጳውሎስ በመንፈስ መሪነት ለዕብራውያን ክርስቲያኖች የጻፈውን ደብዳቤ ያነበበ ማንኛውም ሰው ይህ መጽሐፍ ጠንካራ መንፈሳዊ ምግብ እንደያዘ ማስተዋሉ አይቀርም። ይህ መልእክት እነዚያ ክርስቲያኖች በክርስትና ውስጥ ያለው የአምልኮ ሥርዓት የላቀ መሆኑን እንዲገነዘቡ እንዲሁም በድፍረት መስበካቸውን እንዲቀጥሉ ረድቷቸዋል።—ዕብ. 10:19-23፤ w24.04 6 አን. 15

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2026
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2026 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ