መሳፍንት
5 በዚያን ቀን ዲቦራ+ ከአቢኖዓም ልጅ ከባርቅ+ ጋር ሆና ይህን መዝሙር ዘመረች፦+
3 እናንተ ነገሥታት ስሙ! እናንተ ገዢዎች ጆሯችሁን ስጡ!
ለይሖዋ እዘምራለሁ።
ለእስራኤል አምላክ+ ለይሖዋ የውዳሴ መዝሙር እዘምራለሁ።+
በ40,000 የእስራኤል ወንዶች መካከል፣
አንድ ጋሻ ወይም አንድ ጦር ሊታይ አልቻለም።
ይሖዋን አወድሱ!
10 እናንተ፣ ነጣ ባሉ ቡናማ አህዮች የምትጋልቡ፣
እናንተ፣ ባማሩ ምንጣፎች ላይ የምትቀመጡ፣
እናንተ፣ በመንገድ ላይ የምትሄዱ፣
ይህን ልብ በሉ!
11 የውኃ ቀጂዎች ድምፅ በውኃ መቅጃው ስፍራ ተሰማ፤
እነሱም በዚያ የይሖዋን የጽድቅ ሥራዎች፣
በእስራኤል መንደሮች ውስጥ የሚኖሩ ሕዝቦቹን የጽድቅ ሥራዎች መተረክ ጀመሩ።
የይሖዋም ሕዝቦች ወደ በሮቹ ወረዱ።
12 ዲቦራ+ ሆይ፣ ንቂ፣ ንቂ!
ንቂ፣ ንቂ፣ መዝሙርም ዘምሪ!+
የአቢኖዓም ልጅ ባርቅ+ ሆይ፣ ተነስ! ምርኮኞችህን እየመራህ ሂድ!
13 የተረፉትም ሰዎች ወደ መኳንንቱ ወረዱ፤
የይሖዋ ሕዝቦች ኃያላኑን ለመውጋት ወደ እኔ ወረዱ።
14 በሸለቆው* የነበሩ ሰዎች ምንጫቸው ኤፍሬም ነበር፤
ቢንያም ሆይ፣ እነሱ በሕዝቦችህ መካከል እየተከተሉህ ነው።
15 የይሳኮር መኳንንት ከዲቦራ ጋር ነበሩ፤
እንደ ይሳኮር ሁሉ ባርቅም+ ከእሷ ጋር ነበር።
የሮቤል ቡድኖች ልባቸው በእጅጉ አመንትቶ ነበር።
16 አንተ በመንታ ጭነት መካከል የተቀመጥከው ለምንድን ነው?
ለመንጎቹ ዋሽንታቸውን ሲነፉ ለማዳመጥ ነው?+
የሮቤል ቡድኖች እንደሆነ ልባቸው በእጅጉ አመንትቷል።
አሴር በባሕር ዳርቻ ላይ ሥራ ፈቶ ተቀምጧል፤
በወደቦቹም ላይ ይኖራል።+
ምንም ብር ማርከው አልወሰዱም።+
20 ከዋክብት ከሰማይ ተዋጉ፤
በምሕዋራቸው ላይ ሆነው ከሲሳራ ጋር ተዋጉ።
21 የቂሾን ወንዝ፣
ጥንታዊው ወንዝ፣ የቂሾን ወንዝ ጠራርጎ ወሰዳቸው።+
ነፍሴ* ሆይ፣ ብርቱዎቹን ረገጥሽ።
22 የፈረሶች ኮቴ ሲረግጥ የተሰማው ያን ጊዜ ነበር፣
ድንጉላ ፈረሶቹ በኃይል ይጋልቡ ነበር።+
23 የይሖዋ መልአክ እንዲህ አለ፦ ‘መሮዝን እርገሙ፤
ነዋሪዎቿንም እርገሙ፣
ይሖዋን ለመርዳት አልመጡምና፣
ይሖዋን ለመርዳት ከኃያላኑ ጋር አልመጡም።’
በድንኳን ከሚኖሩ ሴቶች ሁሉ ይልቅ የተባረከች ነች።
25 ውኃ ጠየቀ፣ ወተት ሰጠችው።
ለመኳንንት በሚቀርብበት ጎድጓዳ ሳህን እርጎ ሰጠችው።+
26 እጇን ዘርግታ የድንኳን ካስማ አነሳች፣
በቀኝ እጇም የሠራተኛ መዶሻ ያዘች።
ሲሳራንም ቸነከረችው፣ ጭንቅላቱንም ፈረከሰችው፣
ሰሪሳራውንም ተረከከችው፤ በሳችው።+
27 እሱም በእግሮቿ መካከል ተደፋ፤ በወደቀበት በዚያው ቀረ፤
በእግሮቿ መካከል ተደፋ፣ ወደቀ፤
እዚያው በተደፋበት ተሸንፎ ቀረ።
28 አንዲት ሴት በመስኮት ተመለከተች፣
የሲሳራ እናት በፍርግርጉ አጮልቃ ወደ ውጭ ተመለከተች፣
‘የጦር ሠረገሎቹ ሳይመጡ ለምን ዘገዩ?
የሠረገሎቹ ኮቴ ድምፅስ ምነው ይህን ያህል ዘገየ?’+
29 ጥበበኛ የሆኑት የተከበሩ ወይዛዝርቷ ይመልሱላታል፤
አዎ፣ እሷም ለራሷ እንዲህ ትላለች፣
30 ‘ያገኙትን ምርኮ እየተከፋፈሉ መሆን አለበት፣
ለእያንዳንዱ ተዋጊ አንድ ልጃገረድ* እንዲያውም ሁለት ልጃገረዶች፣*
ለሲሳራም ከምርኮው ላይ ቀለም የተነከሩ ልብሶች፣ አዎ ቀለም የተነከሩ ልብሶች፣
ምርኮውን ለማረኩት ሰዎች አንገት፣
ቀለም የተነከረ ባለ ጥልፍ ልብስ፣ እንዲያውም ሁለት ባለ ጥልፍ ልብስ እየተሰጠ ነው።’
31 ይሖዋ ሆይ፣ ጠላቶችህ ሁሉ ይጥፉ፣+
አንተን የሚወዱ ግን ደምቃ እንደምትወጣ ፀሐይ ይሁኑ።”